Posts

Showing posts from January, 2016

የማካቬሌ ፍልስፍና

Image
እንደአለመታደል ሆኖ ከሌሎች ፈላስፋዎች በተለየ መልኩ ስሙ የተበላሸበት ሰው ነው -ማካቬሊ ፡፡ አንድ ሰው ማካቬሊያን ነህ ካለህ አላማዉን ለማሳካት የማይጠቀመው መንገድ የለም ማለቱ ነው፡፡ ማካቪሊያን መደበኛ ተቀባይነት ያለውን የስነ ምግባር ደረጃ በመጣስ ለግል ጥቅም ሲባል በማጭበርበር ወይም በሴራ በሉት አላማን የሚያሳኩበትን ሂደት የሚያሳይ ሆኖ ዛሬም ድረስ የተሳለ ጥቁር ገፅታ ነው፡፡

የፕሌቶ ፍልስፍና

Image
ፕሌቶን ከቀደምት የግሪክ ፈላስፋዎች ለየት የሚያደርገው በፊት የነበሩት የግርክ ፍልስፍናዎች በተወሰነ መልኩ በአንድ ጉዳይ ላይ ብቻ የሚያጠነጥኑ ሲሆኑ ፕሌቶ ግን  በሁሉም የእውቀት ዘርፎች ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ መስጠት መቻሉ ነበር ፡፡ደህና ደረጃ ከነበራቸው ቤተሰቦቹ ከክርስቶስ ልደት በፊት 427 ም.አ  በአቴንስ የተወለደው ፕሌቶ በምዕራባዉያን ፍልስፍና ታሪክ እጅግ በጣም ጎላ ያለ ቦታ የሚሰጠውና ከሶቅራጥስ ተማሪዎች አንዱ በመሆን ጎልቶ መውጣት የቻለ  ፈላስፋ ነው፡፡

ኢማኑኤል ካንት

Image
ኢማኑኤል ካንት በምዕራባውያን ፍልስፍና ታሪክ የሚሰጠው ድርሻ እጅግ በጣም የጎላ ነው፡፡ የካንት የ80 አመታ ህይወት እጅግ በጣም ጭምት በሆነ ሂደት የተሞላ ነው፡፡ ካንት በዘመኑ ከተወለደባት ፑርሺያ ውጭ እንደሌሎቹ ፈላስፋዎች ከቦታ ወደ ቦታ የመዘዋወር  ልማድ አለመኖር ብቻ ሳይሆን በፖለቲካዊና ማህበራዊ ተሳትፎውም ደካማ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ በነዚህ ሂደቶች ውስጥ ተሳትፎ የጎላ ታሪክ ባይመዘገብለትም በመመህርነትና በፍልስፍና ፀሀፊነት ያሳላፋቸው ጊዚያቶች ከሌሎች ፈላስፋዎች በተለየ መልኩ ከጥበብ አናት ላይ ሊያስቀምጡት በመቻላቸው ካንት ህይወቱን በሙሉ የሰጣት ፍልስፍና አላሳፈረችውም፡፡

ሞት

ሞት ማለት ነብስህ ከአካል ተለይታ ወደ ሰማዬ  ሰማያት የምትሄድበት ዘላለማዊ መለየት ነው። እንቅልፍ ማለት ደግሞ  ነፍስህ ከስጋህ ተለይታ ከጣሪያው ላይ የምትሆንበት ጊዜያዊ መለየት ነው። ጧት ስትነቃ ዱብ ትልና ከስጋዋ ትቀላቀላለች። ስትተኛ ነብስህ ጣሪያ ላይ ሆና ትታዘብሀለች።

ታማኝነት ምንድነው?

ታማኝነት እውነተኛ ነኝ በሚል በአንድ ጉዳይ ላይ ለረጅም ጊዜ መጣበቅ ሳይሆን ከሁኔታዎች ጋር የሚናበብ ኃላፊነት የተሞላበት ማስመሰልም ጭምር ነው። ሌሎች ላይ የእምነት ስሜትን መፍጠር ካልቻልክ የአንተ ታማኝነት ከንቱ ነው። እምነት የሚፈጠረው ደግሞ ለመምስል ያስገደደህን ሁኔታ በግልፅ በማሳየት ነው።

ስነ ልቦና

ለማንኛውም ህይወት የሚሆን ሰብዕና ለመገንባት ሞክር። ህይወት የሚሊየን ክስተቶች ውጤት እንደሆነች እወቅ። የህይወትን ክስተቶች በአንድ ሰብዕና መጋፈጥ እንደማይቻል ተገንዘብ። የህይወትን የድምቀት ደረጃ ተከትሎ የሚተውን ሁለገብ የስነ ልቦና ይዘት ይኑርህ።  ሲጨልም የሚያበራ፣ ሲደምቅ ከብርሀን የምትከላከልበት ሰብዕና ለመገንባት ሞክር።

ሚዛናዊ አስተሳሰብ

ሚዛናዊ አስተሳሰብ የሚዛናዊ ህይወት መሰረት እንደሆነ አስብ። የአንድ አስተሳሰብ እስረኛ አትሆን። የሰው ልጅ ብስለት የሚለካው አንድ አስተሳሰብ ላይ ሙጥኝ በማለት ሳይሆን የተለያዩ አስተሳሰቦችን በብቃት ማስተናገድ የሚችል አእምሮ በመገንባት እንደሆነ እወቅ።

የአምላክ ታሪክ

Image
አምላክ የሚለው ቃል ሁሉን ማድረግ የሚችል፣ ፍፁማዊና ዘላለማዊ ህልውና ያለው የሁሉም ነገሮች ምንጭ የሆነ አካል የሚለውን ፅንሰ አሳብ በሚወክል መልኩ ማስቀመጥ ይቻላል፡፡ ለአምላክ የተሰጠው ገፅታ አምላክ የወንድ ጾታ ያለው፣  ሩህሩህ፣ መሀሪ ፣ ደግ የመሳሰሉትን የሰው ባህሪያት በማስቀመጥ ከሰው ልጅ ጋር በሚመሳሰል መልኩ ሲቀመጥ  በሌላ መልኩ ደግሞ አምላክ የሰው ልጅ የያዛቸውን ባህሪያት ዉጪ የሆኑ ባህሪያት ባለቤት እንደሆነ የሚያስረዱ ገጽታችም ይቀመጣሉ፡፡

የታሪክ ሽሚያ

በቅርቡ ኢህአዴግ የኢትዮጵያን  ታሪክ ተጠያቂነትን በሚያከፋፍል መልኩ ቀምሮ አቀረበ። የታሪክ ትንተናው ዛሬ ያለችው የተጎሳቆለች አገር የኔ ውጤት ሳትሆን  ከባለፉት ስርአቶች እየተጎተተ የመጣ ችግር የፈጠራት እንደሆነች እወቁልኝ ነው። በእርግጥ እኔም እንደማምነው የኢትዮጵያ ችግር ፈጣሪ ኢህአዴግ ብቻ አይደለም። የዛሬው ችግር ትናንት መሰራት የነበረባቸው የቤት ስራዎች ባለመሰራታቸው የመጣ ችግር ነው። ይሁን እንጂ ታሪክ የመሻማት አይነት ነገር እያየሁ ነው።

ውሸት አልወድም የሚል ውሸት

ውሸት አልወድም ማለት በራሱ ውሸት ነው። ሁሉም የራሱን ስሜት እውነት አድርጎ በሚረዳበት አገር እውነት የሚፈልግ ሰው የለም። ከእውነት ይልቅ የሚፈልገው ነገር ቢኖር ራሱ ከፈጠረው ውሸት ውስጥ እውነት የሚመስል ነገር ነው።

ማንን ነው የምንከተለው: እውቀት ወይስ ሰው?

ቅልብጭ ባለ አማርኛ እውቀት ማለት የእውነት  የአስተሳሰብ ውክልና ማለት ነው። እውነት ደግሞ የመሆን ህልውና ውክልና ማለት ነው። በእውነት ትርጉም ላይ የሚሰጠው አሳብ አንፃራዊ ቢሆንም የእውቀትን ትርጉም ተጨባጭ በሆኑ መለኪያዎች ፈትሾ ማስቀመጥ ይቻላል። እውቀት ማለት ሰው ማለት አይደለም። እውቀት እና አዋቂ ይለያያሉ።

ዲዮገንስ ውሻው ፤ አስገራሚ የጥበብ ህይት

Image
ታሌስ ላይ በሚጀምረው የጥንታዊ ግሪክ ፍልስፈና ታሪክ ከአርስቶትል ሞት በኋላ  ገነው ከወጡ የፍልስፍና ዘዉጎች መካከል  የሲኒስዝም ፍልስፍና አንዱ ሲሆን የዚህ ፍልስፍና ፈላስፋዎች ሕይወትን እንደወረደ ተፈጥሯዊ በሆነ መልኩ መኖር እንደሚገባ የሚያስተምሩ አኗኗራቸውም ከማህበረሰቡ የመገለልና ራስን ነፃ አድርጎ ቀለል ያለ ህይወት በመምራ ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡ ፡ በዚህ የፍልስፍና ጊዚያት የታላቁ እሰክንድር የመስፋፋት ዘመቻ ተከትሎ የግሪክ ፍልስፍና ከሌሎች ማህበረሰብ ፍልስፈናዎች ጋር እራሱን እየደባለቀ የመጣበት ሁኔታ ነበር፡፡ በዚህ ጊዚያት ከተነሱ ፈላስፋዎች መካከል ዲዮጋንስ ውሻው የሚባለው አስገራሚ የጥበብ ሕይውት ያለው ሰው ነበር፡፡

ድብቅ በቀል

ድብቅ በደል የሚታወቀው ተበዳይ በዳይን መልሶ ሲበድለው ነው። በግልፅ ይቅር የሚሉህን በልብህ አክብራቸው። በድብቅ የሚበድሉህን በአደባባይ አዋርዳቸው። በድብቅ መበደል ከይቅርታ ይልቅ የሚቀናው በአደባባይ ለመበደል ነው። አንዳንድ ሰው ጓደኛ የሚሆንህ እሱ በሚፈልገው ሁኔታ ነው። እሱ ሲፈልግ ይቀርብሀል። ካልፈለገ ይርቅሀል። እሱ በሚፈልግበት መልኩ ጓደኛ ይሆንና እሱ በሚፈልግበት ሁኔታ ስትፈልገው አንተ በምትፈልገው መገኝት አይፈልግም። እሱ በሚፈልገው እዲገኝ መፈለግ እሱ ካልፈለገ ስህተት ነው። ይህ አንዱ ድብቅ በደል ነው። ጓደኝነት ሁለት አይነት ጉድኝት ነው። አንደኛው አካላዊ ጉድኝት ፣ ሁለተኛው የስሜት ውህደት። ከአካላዊ መሰባሰብ ይልቅ የስሜት ውህደት ንፁህ ለሆነ ጓደኝነት አስፈላጊ ነው። አንተ ስሜትህን የሰጠኸው በአካሉ ከአንተ ተገናኘ። አንተ ስሜትህን ሳስት እንድትሰጠው አድርጎ የራሱን ስሜት ከሰሰተ ከዚህ በላይ ክህደት ምን አለ? በጓደኝት ውስጥ የሚኖርህ የተሳትፎ ዋጋ እየቀነሰ ከሄደ የአንተ በጓደኝነቱ ውስጥ መቀጠሉ አስፈላጊነት ተሸረሸረ። በጓደኝነቱ ውስጥ በተቻለ መጠን ተሳትፎህን ዝቅ ላለማድረግ ሞክር። ከጓደኞችህ ጋር ተመጣጣኝ ተሳትፎ ማድረግ ካልቻልክ አንተ ጓደኛቸው ሳትሆን አሸንጉሊታቸው ነህ። እሱ በሚፈልገው መልኩ ሁልጊዜ የምትገኝለት  ጓደኛህ አንድ ቀን አንተ በምትፈልገው መልኩ ለመገኘት የማይፈልገውን መሆን ካልፈለገ፣ እሱ የአንተ ጓደኛ አንተ ደግሞ የሱ አሻንጎሊት ነህ። ከአንተ ምንም አልፈልግም ብሎ ሳይፈለጉ መፈለግ በራሱ የሆነ ነገር መፈለግን  የሚያሳይ ፍላጎት ነው። ሌላው ድብቅ በደል ምንድነው? እሱ ሲፈልግ በብዙ ቀርቦህ ፣ እሱ በቀረበበት ቀረቤታ ለመቅረብ ስትፈልገው የሚርቅህ ሰው በድብቅ እየበደለህ ነው። በጓደኝነት ውስጥ ከባ...

ግልፅነት ለጓደኝነት

በጓደኝነት ውስጥ ግልፀነት አስፈላጊ ነው። አንተ ግልፅ ሆነህ የቀረብከው ጓደኛ፣ ከአንተ የሚደብቀው ነገር ከበዛ ፣ ጓደኝነቱን ሲጨርስ  ጠላት ለመሆን አስቀድሞ እያመቻቸ ነው። እሱ በሚሰማው መልኩ ጓደኛ እንድትሆን የሚፈልግን ሰው አንተ የሚሰማህን እንዲሰማው ማድረግ የምትችለው እንዲሰማው የማይፈልገውን እንዲሰማው ማድረግ ስትችል ነው። በጓደኝነት ውስጥ ታማኝነት የሚለካው በቃል የተናገሩትን በተግባር ለመተርጎም በሚደረግ ጥረት ነው። ይህ ካልሆነ ግን በተግባር መተርጎም የማትችለውን ነገር በቃል አለመናገር በራሱ ታማኝነት ነው። ጓደኛህ ስትፈልገው መቅረብ ካልቻለ ፣ ሳትፈልገው መራቅ ካልቻልክ የሚኖርህ አማራጭ በፈለገህ ጊዜ ቀርበኸው  ፣ ባልፈለከው ጊዜ ማራቅ ነው። በጓደኝነት ውስጥ በደስታ ጊዜ አንድ ላይ እንደመጫወት የመሰለ ጣፋጭ ነገር ፣ በችግር ጊዜ ለብቻ መጣላትን የመሰለ መራራ ነገር የለም። በደስታ ጊዜ አብሮህ የተደሰተ ጓደኛ ፣  በችግር ጊዜ አብሮ ሆኖ ካልተጣላህ ፣ መጀመሪያም ከአንተ የሚፈልገው ጓደኝነት ሳይሆን የራሱን የህሊና ምቾት ነው። በደስታ ጊዜ አብሮህ ሆኖ ተጣልቶ የማይለይህ ከጓደኝነታችሁ በላይ ራሱን ጓደኛ ያረገ ነው። ጓደኞችህ እንደሚወዱህ ቢነግሩህም መውዳዳቸው ትክክል የሚሆነው አንተን እንደወደዱህ እንዲሰማህ ማድረግ ሲችሉ ነው።እንወድሀለን በሚሉት ደረጃ መውደዳቸው ካልተሰማህ በአካልህ በጓደኞችህ መሀል ብትሆንም በስሜትህ ግን ብቸኛ ነህ። የጓደኛህ ችግር መረዳት ያለብህ ጓደኛህም የአንተን ችግር መረዳት ከቻለ ነው። የአንተን ችግር መረዳት ያልቻለን ጓደኛ ፣ ችግሩን ለመረዳት የምትገደድ አለመሆኑ በራሱ ሊረዳልህ የሚገባ ችግር ነው። የአንተን ስሜት ሳይጠብቅ የእሱን ብቻ ስሜት እንድትጠብቅለት የሚፈልግ ጓደኛ፣ የአንተን ስሜት ...

ይቅርታ

ይቅርታ በራሱ ምንም ነው። የይቅርታ ዋጋ የበደል መኖር ነው። በስህተት በደል የይቅርታ ዋጋ በገንዘብ ቢተመን የትዬለሌ ነው። ከምንም ነገር በላይ ይቅርታ የሌለው ስህተት ቢኖር ይቅርታን አጥፍቶ እንደተበደሉ በበደል መኖር ነው።

ስለፍቅር

Image
ከሁሉም በፊት ለፍቅር ቅድሚያ መስጠት ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው። ሌላውን የማፍቀርና ያለማፍቀር መብት የሚወሰነው ራስን ከማፍቀር ግዴታ ነው።

የኢትዮጵያ ታሪክና የኦሮሞ ህዝብ

በግርድፍ የዳሰሳ ጥናት ከአምስት የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች አራቱ የኢትዮጵያ ታሪክ የባለቤትነት ስሜት የለሌላቸው ሲሆን ከአምስቱም አምስቱ በኢትዮጵያ ታሪክ  የኦሮሞ ህዝብ በተለዬ መልኩ እንደበተደለ

ትችት እንደ ስድብ

ለኔ ስድብ ሆኖ የሚሰማኝ ሌላው ስድብ ብሎ የሚጠላው ቃል አይደለም ።ለምሳሌ ውሻ  ለኔ የስሜት ውክልና ነው። ቃሉን የምወስደው እኔ ለቃሉ በምወክለው ስሜት ደረጃ ነው። ስለዚህ በስድብ ስሜት ካልወከልኩት ውሻ መባል ለኔ ስድብ አይደለም። ስድብ ለኔ ሌላ ምንም አይደለም።ስድብ

ልማት የማን ነው?

በመርህ ደረጃ ልማት የህዝብ መብት ነው። ለመንግስት ደግሞ ግዴታ ነው። ነገር ግን ልማት የህዝብ መብት ነው ሲባል ህዝብ ልማት የመጠየቅ መብት አለው ማለት እንጂ በግልባጩ ልማት አልፈልግም የማለት መብት አለው ማለት አይደለም። ይህ አይነት የህዝብ ዝንባሌ ከተፈጠረ ልማት የማስፈን ጉዳይ የመንግስት መብት ይሆናል። መንግስት ማለት መንግስታዊ ስርአቱ በመሆኑ የልማትን ጉዳይ የመወሰን መብት የስርአቱ መብት ይሆናል።

አቅጣጫው የጠፋበት ትውልድ

በምእራባውያን አገራት ያለው ኢትዮጵያዊ ትውልድ የጉዞ አቅጣጫው የጠፋበት የማንነት ከርታታ ነው። በአንድ በኩል የሚኖርበት አገር ውስጥ ያለ ፈጣን ለውጥን እግር በእግር ተከትሎ ከፍጥነቱ ልክ መራመድ ያቃተው በሌላ በኩል ወደኋላ ጥሎት የሄደውን ማንነት የሚጎትተው ቢሆንም ወደዚህ ማንነት ለመመለስ የብቃት ችግር ውስጥ የሚገኝ ተቅበዝባዥ ትውልድ ነው።

ሰው መሆን

ሰው መሆን በስጋ ሳይሆን በአስተሳሰብ ነው። ሰው አስተሳሰቡ እየዳበረ ካልሄደ ደም የሚንሸራሸርበት ድንጋይ ነው። ትንሽ ከፍ ካደረግነው  ማሰብ እየቻለ ካላሰበ ሰውም ከብት ነው። የሰው ልጅ ጊዜው ከሚጠይቀው ለውጥ ጋር የሚመጣጠን አስተሳሰብ ይዞ መገኘት ካልቻለ፣ የሚኖርበትን ቦታ ለህልውናው ምቹ ማድረግ የሚያስችል የአስተሳሰብ ምንጭ መሆን ካልቻለ ከከብት በምን ተሻለ?

የኢትዮጵያ ታሪክ: እንደሆነው ወይስ እንደሚመስለው?

  በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ያለኝ አመለካከት በጥርጣሬ የታጀበ (sceptical) ሊባል የሚችል ነው። ሌላውን ኢትዮጵያዊ አሳመነም አላሳመነ ለዚህ አመለካከት መፈጠር ምክንያት የሆኑኝን አሳቦች ማስቀመጥ እችላለሁ።

የፖለቲካ ትግል መለኪያ

Image
የፖለቲካ ትግል ስኬት የሚለካው በፈጠረው የብዙሀን ግርግር ሳይሆን በብዙን ላይ ባመጣው የአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ስር የሰደዱ ችግሮችን ወቅታዊ በማድረግ የተለየ ቀለም ሰጥቶ የብዙሀንን ግርግር መፍጠር የፖለቲካ ትግል ደረጃ የሚመጥን አይደለም።

በኢትዮጵ ታሪክ መቻቻል ወይ?

በኢትዮጵያ ታሪክ መቻቻል ነበረ ወይ? ብዙ ሰው በተሳሳተ መንገድ ምላሽ የሰጠው ጥያቄ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ተቻችለውና ተከባብረው የኖሩ ህዝቦች ናቸው የሚለው ብሄል ከተረት ያለፈ ዋጋ የለውም። በተዝካር፣ በፅዋና መሰል ድግሶች አንድ ላይ መብላትና መጠጣት መቻቻልን ሊያመላክት አይችልም።

ለዘብተኝነት: የከሸፈ የፖለቲካ አቅም

Image
በአገሪቱ የአጭር ጊዜ የዴሞክራሲ ተሞክሮ ውስጥ ብልጭ ብሎ የጠፋ የሚመስል የፖለቲካ ትግል አካሄድ ነበር። በትግል አካሄዱ መሀል ሰፋሪ የሚባለው የፖለቲካ አካሄድ ከሁለት  ጫፎች መካከል የሚገኝ ሚዛናዊ የሆነ የፖለቲካ አካሄድ ነው።

በቬገንስታይን እይታ: ፍልስፍና ምንድነው?

Image
"ፍልስፍና ምንድነው?" የሚለው ጥያቄ በርካታ ፈላስፋዎችን በልዩነት ያፈላሰፈ ጉዳይ ነው። ይሁን እንጂ ሁሉም ፈላስፋዎች በፍልስፍና ባህሪ ላይ የሰጡት ትርጉም ሰፊ ልዩነት ያለው ነው። ለምሳሌ:

የመንጋ ሙህርነት

  እውነት የምትቆመው ተገታትለው በሚከተሉ የመንጋ ድጋፍ ሳይሆን በራሷ የጥንካሬ ብቃት ነው። በመንጋ አጀብ የሚመራ ሙሁር የሰካራም ስሜት የሚያዝናና የጠጅ ቤት አዝማሪ ማለት ነው። ከመንጋው ፊት መሰለፍ የሚያሳየው መሪነትን ሳይሆን ለመሻማት የሚያመች ቦታን መምረጥ ነው።